በዚህ ገጽ በተለያዩ ታዋቂ ገጣሚያን የተጻፉ የአማርኛ ግጥሞች ያገኛሉ
| መሸ ደግሞ አምባ ልውጣ! አምባ ወጥቼ እኩለ-ሌት ፤ ስለት ገብቼ በስሟ ከርሞ ሰይጣን በሷ አስቶኝ፤ ልገላገል ከህመሟ ጠበሏ አፋፍ በጨረቃ፤ ደጋግሜ፤ ማህሌት ቆሜ ሆዴ ቃትቶ ባር ባር ብሎ፤እርቃኔን ከሷ ታድሜ ደጀ ሰላሟን በአራት እግር፤ ተንበርክኬ ተሳልሜ በስጋዬ እሚነደውን፤ በጸሎት ላቤ አጣጥሜ እፎይ ብዬ አመስግኜ፤ ውዳሴዋን ደጋግሜ... ገና ከደጅዋ እልፍ ሳልል፤ ደሞ ይምጣ የቁም ህልሜ? ሌት በጥምቀቷ የነጣው፤ ነጋ፤ ደፈረሰ ደሜ። ለሷ እንጂ ለኔ አልያዘልኝ፤ አዬ የስለት አታምጣ! በውጣ ውረድ በጠበል፤ ባሣር ወዜ ቢገረጣ ልክፍቷ እንደሁ አልለቀቀኝ፤ መሸ ደሞ አምባ ልውጣ! ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድሀን፣ እሳት ወይ አበባ! | መሆን አለመሆን በመሆን እና ባለመሆን በማድረግ እና ባለማድረግ በሁለት ታዛዦች ስር መውደቅ ነው ሰው የመሆን ትልቅ ህግ ሊኖሩት በማይፈቅዱት ህግ ሊፈጽሙት በማይሹት ስህተት በጣምራ ግጭቶች መሃል መቆም ነው ሰው የመሆን ሰውነት ይሄ ሁሉ ፍጡር ይሄ ሁሉ ፍጡር በፍጥረት መድረክ ላይ የሚርመሰመሰው ላንዲት ቅጽበት እንካን ሰው ሆኖ አያውቅም ሰው ሊሆን ጽንስ ነው ሰው እስኪሆን ድረስ አንዳንድዜ አምላክ አንዳንዴ ሰይጣን ነው። ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን | መሄዴ ነው ባር ባር አለው ሆዴ ልቤ መሬት ለቆ ሊያከንፈኝ እንዳይሆን አለግብሩ መጥቆ አለአስተዳደጉ አለባህሉ ወድቆ ሽው እልም ሽው እልም ልቤ ወፌ ይላላ በመስተፋቅር ቀስት በሮሮ ምህላ እንደደመና አክናፍ እንደጮራው ጥላ ሽው እልም ሽው እልም ሽው እልም ይላላ ነሸጠው ሸፈጠ ሄደ ሸመጠጠ በመስተፋቅር ቀስት በሮሮ አመለጠ። ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን | ክልክል ነው
| |
| «በጠራ ጨረቃ» በጠራ ጨረቃ በእኩለ ሌሊት አይኖቿ እያበሩ እንደ ከዋክብት «ሳማት ! ሳማት !» አሉት «እቀፍ ! እቀፋት።» አላወላወለም ወጣቱ ታዘዘ ወገቧን አንገቷን እጇን በእጁ ያዘ ምንም እንኳ ጡቷ እንደሾህ ቢዋጋ ጣቷ በመሆኑ የጉማሬ አለንጋ ጆሮ ግንዱን ሰማው በጥፊ ሲናጋ። ዋ ጀማሪ መሆን ! ዋ ተማሪነት ዋ ትእዛዝ መፈጸም ዋ ምክር መስማት ! በጠራ ጨረቃ በኩለ ሌሊት... መንግስቱ ለማ | ወሰደው ከፊትዋ ልጅነት ሆነና ዕረፍት የሌለበት አንገት ያለሃሳብ የሚመዘዝበት ልብ ከግንባር ላይ የሚነበብበት ለጋነት ባጠራው ይሉኝታ ቢስ ፊትዋ በስልት ያልተገራው ግልጽ አስተያየትዋ መልሶ ቢያሳየው የራሱን አንካሳ የባህሉን ጅራፍ የወጉን ጠባሳ “ምነው ዓይን በላች ይሉኝታ አጣችሳ”“ እያለ ጮኸና ልቧን አስበርግጐ ወሰደው ከፊትዋ ልጅነትዋን ጠርጐ በሞረድ ምላሱ ፈግፍጐ ፈግፍጐ . . . (ታገል ሠይፉ፣ ቀፎውን አትንኩት፣ 1986) | ጠላቴን ስመርቅ
| ደመወዙን ቢጥል አንስተው ጠጡበት ባርኔጣውን ቢጥል ወስደው ደመቁበት ከዘራውን ቢጥል ተመረኮዙበት በሄደበት ሁሉ እየተከተሉ በጣለው ሲያጌጡ በጣለው ሲያተርፉ ራሱን ሲጥል ግን አይተውት አለፉ በውቀቱ ስዩም (ካንድምታ ላይ የተወሰደ ) | |
ፍቅር ጥላ ሲጥል 1998፡ 96-97
| ያንድ አፈር አፈሮች ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
| ሃገሬ አገሬ ውበት ነው ለምለምና ነፋስ የሚጫወትበት ጸሃይ የሞላበት፣ ቀለም የሞላበት። አገሬ ቆላ ነው፣ ደጋ ወይና ደጋ እዚያ ብርሃን አለ ሌሊቱ ሲነጋ። አገሬ ተራራ ሸለቆ ረባዳ አገሬ ጅረት ነው ገደልና ሜዳ። ውሸት ነው በበጋ ጸሃይ አትፋጅም ክረምቱም አይበርድም፣ አይበርድም፣ አይበርድም። አገሬ ጫካ ነው እንሰሳት አራዊት የሚፈነጩበት በወጥመድ ሳይገቡ ሳይነካቸው ጠላት። እዚያ አለ ነጻነት። በሃገር መመካት፣ በተወላጅነት፣ በባለቤትነት፣ እዚያ አለ ነጻነት። አገሬ ሃብት ነው። ጎመኑ ስብ ጮማ፣ ቆሎ ክትፎ ስጋ ድርቆሹ ፍትፍት ነው፣ ቃሪያው ሙክት ሠንጋ። ጠጁ ነው ወለላ ከኮኛክ ይነጥቃል የመንደሩ ጠላ። እህሉ ጣዕም አለው እንጀራው ያጠግባል በዓሉ ይደምቃል፣ ሙዚቃው ያረካል፣ ጭፈራው ዘፈኑ ችግርን ያስረሳል። እዚያ ዘመድ አለ። ሁሉም የናት ልጅ ነው፣ ሁሉም ያባት ልጅ ነው፣ ጠላትም አንዳንዴ ይመጣል መቃብር ባለጋራም ቸር ነው “ያገር ልጅ ሲቸገር” ። ገነት ነው አገሬ። ምነው ምን ሲደረግ ! ምነው ! ለምን ! እንዴት ! ዘራፊ ቀማኛ ምቀኛ ወንበዴ ጥርኝ አፈር በጁ ስንዝር ወሰን አልፎ የተቀደሰውን ያፍሪቃ ላይ ደሴት ባያገኝ ለማርከስ ጠላት ይመኝ እንዴት። እምቢኝ አሻፈረኝ ! አሻፈረኝ እምቢ ! መቅደስ ነው አገሬ፣ አድባር ነው አገሬ። እናትና አባት ድኸው ያደጉበት ካያት ከቅደመ አያት የተረካከቡት አፈር የፈጩበት፣ ጥርስ የነቀሉበት። አገሬ ዓርማ ነው የነጻነት ዋንጫ በቀይ የተጌጠ ባረንጓዴ ብጫ። እሾህ ነው አገሬ፣ በጀግናው ልጅ አጥንት የተከሰከሰ ጠላት ያሳፈረ አጥቂን የመለሰ። አገሬ ታቦት ነው መቅደስ የሃይማኖት ዘመን የፈተነው በጠበል በጸሎት። ለምለም ነው አገሬ፣ ውበት ነው አገሬ፣ ገነት ነው አገሬ። ብሞት እሄዳለሁ ከመሬት ብገባ እዚያ ነው አፈሩ የማማ ያባባ። ስሳብ እሔዳለሁ ቢሰበርም እግሬ አለብኝ ቀጠሮ ከትውልድ አገሬ። አለብኝ ቀጠሮ ከትውልድ አገሬ ካሳደገኝ ጓሮ። ገብረክርስቶስ ደስታ። | ||
እውነት ለፈለገ....
| ድምጽ አልባ ፊደላት
| መቃብሬ ላይ 'ሚጣፍ ኑረዲን ዒሣ
መሞዘቅ ኑረዲንኢሣ
|
ስለወሬ ቁመት ኑረዲን ዒሣ
ሐዘን
|
እኔ ጉልት ስውል ጉልት ይውላሉ
| ከጎራው ዘልቄ እስኪ ልነጋገር ካለሰው ቢወዱት ምን ያደርጋል አገር? የኔ ውብ ከተማ ሕንፃ መች ሆነና የድንጋይ ክምር የኔ ውብ ከተማ መንገድ መች ሆነና የድንጋይ አጥር
| ||
Create a free website at Webs.com